Announcement የፕረስ መግለጫ ከምሥራቅ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ

የፕረስ መግለጫ ከምሥራቅ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ

-
|
04:30 PM - 04:30 PM

የፕረስ መግለጫ

ከምሥራቅፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ

ምሥራቅ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ11 ዲፓርትመንትበተለያዩ ሙያዎች ያሰለጠናቸውን 850 ሰልጣኞች የምርቃትስነ- ስነስርዓት በነገው እለት በሚሊኒየም አዳራሽ ያካሂዳል፡፡

ኮሌጁ ውጤት ተኮር ስልጠና በመስጠት ውጤታማ፣ በራሱየሚተማመን ፣ ብቁ የፈጠራ ችሎታ ያለው እና በስራ ገበያ ተፈላጊ የሆነ የሰው ሃይል በማፍራትየኢንዱስትሪውን የሰለጠነ የሰው ሀይል ፍላጎትለማሟላት በለያዩ የሙያ ዘርፎች ሲያሰለጥን መቆየቱ ይታወቃል፡፡

በነገው እለት መስከረም 10/2017 ዓ.ም ከደረጃ ሁለት እስከ ደረጃ አምስት በተለያዩየሙያ ዘርፎች ስልጠናቸውን የተከታተሉ 850 ሰልጣኞችንበሚሊኒየም አዳራሽ ያስመርቃል፡፡

መስከረም 10/2017 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ በሚያካሂደው የምርቃት ስነ-ስርዓትየአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ክብርት ወ/ሮ አዳነች አበቤ፣ በምክትል ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ሀላፊክቡር አቶ ጥራቱ በየነ እና ሌሎች የከተማዋ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች፣ የኮሌጁ ዲኖች እና አሰልጣኞች እንደሚገኙ ይጠበቃል፡፡

Copyright © All rights reserved.

Created with